አዕምሮህን አሰራው
እንደ ሰው አዕምሮ ሰነፍ የለም፡፡ ካስተኛቹት መንቃት ፤መነሳት ፤ መስራት ፤ መለወጥ የማይወድ ነገር ቢኖር የሰው ልጅ አዕምሮ ነው፡፡ ሌሊቱን ሙሉ ፊልም ብትጋብዙት ፤ ካፌ 6 ሰዓት ብታስቀምጡት ፤ኢንተርኔት ላይ ቀኑን ሙሉ ብትጥዱት ፤ ምን አለፋቹ ተነስተህ ዙር ብትሉት የማይደክም ማሽን ነገር ነው፡፡ ግን እስቲ 1 መፅሐፍ እንብብ በሉት ፤ 10 ገጽ ሀሳብህን ጻፍ በሉት ፤ ጠዋት ስፖርት ስራ በሉት፤ ቁጭ ብለህ ስራህን አቅድ በሉት በጣም ሰነፍ ነው፡፡
አዕምሮአችን አረም ማብቀል ይቀለዋል፡፡ ነገር ግን በጥበብ የገፉት ሰዎች ያሸንፉታል…..ማሰብ ፤ መስራት ፤ ብርታትን ያስለምዱታል፡፡ ያን ጊዜ ግን መተኛት አይወድም ፤ አሮጌ ነገር አይፈልግም ፤የለውጥ ረሀብተኛ ይሆናል፤መስራት ሲጀምር፤ ሰርተን እስካልጨረስን ድረስ እኛኑ እረፍት ይነሳናል። ማንበብ አዕምሮን ያዳብራል፣ ንቃተህሊናን ያሳድጋል፣ የተሻለ ሰው ያደርጋናል።
Responses