ማንበቤ ብርሀን ሆኖኛል
ለንባብ የሰጠሁት ጊዜ ከመባከን ታድጎኛል። ማንበቤ የትላንት ንግግሬ ከዛሬ ተግባሬ እንዲሰምርልኝ፤ ቃላቶቼ ሀሳቤን እንዲሸከሙልኝ፣ የልብ ዓይኖቼ አርቀው እንዲያዩልኝ፣ ክፉንና ደጉን ፣ ተንኮልና ጥፋቱን እንዲለዩልኝ ብርሀን ሆኖኛል። በማንበቤ ልቤ ሰፊ ሆኖልኛል፣ ሲዋሹኝ፣ሲያሞኙኝ ይታወቀኛል፤ ሲገፋኝ እንዳልንገዳገድ፣ ሲጥሉኝ እንዳልወድቅ ትከሻዬን አስፍቶ ክንዴን አጠንክሮ፣ ሀይልን አላብሶ፣ መንፈሴን አበርትቶልኛል። ማንበቤ በመጠን መኖርን፣ በልክ መናገርን፣ በሚዛን መስፈርን፣ ለክቶ መቁረጥን አድሎኛል።
Responses