በቀላል አልተገነባም!!!!

በንባብ ያዳበርኩት፣ በምክርም ያጸናኹት እውቀት እንዲሁ በቀላል የገነባሁት ልምምድ አይደለም። ለእኔ  ስነልቦና መገንባት፣ ለነገሮች ያለኝ ክብደት ሚዛኑን የጠበቀ ያልተጋነነና ያልተዛባ እንዲሆን ማድረግ የቻልኩት፣ የሰዎችን ልክ ማወቄ፣ የራሴንም ክብር ማስጠበቄእንዲሁ በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ማንበብ በሕይወት የተፈተንኩበት፣ ከሰው የተገለልኩበት፣ ቢሆንም ባገኘሁት ጥልቅ የህይወት ዘይቤን የመረዳት ሚስጥር አትርፌበታለሁ።የቡና ስብሀቱ መፋጀቱ እንደሚባለው  የማንበብ ትሩፋቱ አይን ገላጭነቱ ብዬ በማንበብ ራሳችሁን ፈልጋችሁ አግኙ የዕለቱ መልዕክታችን ነው።

Related Articles

እንዲህ አነባለሁ!

እንዲህ አነባለሁ! • በራእዬ እና በምከታተለው ዓላማዬ ዙሪያ ዘወትር አነባለሁ! • የእኔን፣ የቤተሰቤን፣ የንግዴን፣ የመስሪያ ቤቴንና የሃገሬን ሁኔታ በሚያሻሽል ርእስ ዙሪያ ዘወትር አነባለሁ! • ያነበብኩትን…

ህይወት በማንበብ ትዋባለች፣ ታብባለች፣ ትፈካለች።

ህይወት የምትሸነፈው በትምህርት ብዛት ወይም ረቂቅ እውቀቶችን በመረዳትብቻ አይደለም። ኑሮን የተሻለ ለማድረግ የመጀመሪያው እርምጃ እራስን የተሻለ አድርጎ መገኘት ነው። በአካል፣ በአስተሳሰብ፣ በስነልቦና፣ የአላማ ሰው በመሆን…

ለማንበብ ጊዜ ስጡ!!!!!

ለማንበብ ጊዜ ስጡ። ስታነቡ እያያችሁት የህይወታችሁ ዘይቤ ሲሻሻል፣ ለነገሮች ያላችሁ አረዳድና አመለካከት ሲቀየር ታዩታላችሁ፣ ከጥድፊያና ከስሜታዊ ውሳኔ ትርቃላችሁ፣ በማንበብ ከምታገኙት እውቀት፣ ልምድና ተሞክሮ በመነሳት  ለሚገጥማችሁ…

የህይወታችን መዓዛ

ማንበብ ለህይወታችን የሚሰጠው መዓዛ፣ የሚፈጥርልን ልዩ ስሜት፣ የሚያጎናፅፈን ነፃነት በቃላት ተሰፍሮ የሚያልቅ አይደለም። መፀሀፍት በየትኛውም ደብዛዛ ዘመን ጊዜን የማፍካት ጉልበት ያላቸው፤የህይወት ቅመም ናቸዉ። ማንበብ አንድ ከሚበራ ሻማ ላይ ወደ ሌላ ቁራጭ ሻማ ብርሀን ቢለኮስ፤ ሲበራ የነበረዉ ሻማ እንደማይጠፋ ሁሉ፤ አንባቢ ደግሞ ከንባቡ ያገኘውን እዉቀት በማካፈል በሌላ ሰዉ ህይወት ዉሰጥ የሚበራ ሻማ እንዲሆን ሀይልን ያቀዳጃል። እኛም ከበዛብን የስራ ጫና፣ ከሚፈታተነን የህይወት አዙሪት…

Responses