የህይወታችን መዓዛ

ማንበብ ለህይወታችን የሚሰጠው መዓዛ፣ የሚፈጥርልን ልዩ ስሜት፣ የሚያጎናፅፈን ነፃነት በቃላት ተሰፍሮ የሚያልቅ አይደለም። መፀሀፍት በየትኛውም ደብዛዛ ዘመን ጊዜን የማፍካት ጉልበት ያላቸው፤የህይወት ቅመም ናቸዉ። ማንበብ አንድ ከሚበራ ሻማ ላይ ወደ ሌላ ቁራጭ ሻማ ብርሀን ቢለኮስ፤ ሲበራ የነበረዉ ሻማ እንደማይጠፋ ሁሉ፤ አንባቢ ደግሞ ከንባቡ ያገኘውን እዉቀት በማካፈል በሌላ ሰዉ ህይወት ዉሰጥ የሚበራ ሻማ እንዲሆን ሀይልን ያቀዳጃል። እኛም ከበዛብን የስራ ጫና፣ ከሚፈታተነን የህይወት አዙሪት በተለየ መልኩ ለማሰብ እንድንችል በተጣበበ ጊዜም ቢሆን ዕለት ዕለት ጥቂት እናንብብ፣ አንብበንም ስብዕናችንን እንገንባ፣ ማንነታችንን እናስውብ። መልዕክታችን ነው።

Related Articles

ለዚህ ነው ማንበብ የሚያስደስተኝ፣ አንባቢ ሰው የሚያስቅቀናኝ፣ መጽሀፍት የሚያጓጉኝ!!!

አንባቢ ሰው አንባቢ ሲናገር አይደነቃቀፍም፤ ሃሳብ አይነጥፍበትም። እንዲያውም ቃላት ለሃሳቦቹ ይሰግዳሉ። ቋንቋ ይታዘዘዋል። የቃላት ሃብቱ ንግግሩ በጉጉት እንዲደመጥ ይጎተጉታሉ። አንባቢ ሰው ትልቅ የሃሳብ ጎተራ አለው።…

ማንበብ ወደ ስክነት የሚመራ የእረፍት መንገድ ነው።

ማንበብ ወደ ስክነት የሚመራ የእረፍት መንገድ ነው። ስታነብ የማወቅ ጉጉትህ ይጨምራል፣ የመጠየቅ ፍላጎትህ ይነሳሳል፣ የሰዎችን ሀሳብ ለመረዳት የሚያስችል የመከባበር አቅም ታጎለብታለህ፣ በማንበብ ውስጥ ራስህን ፈልገህ…

ህይወት በማንበብ ትዋባለች፣ ታብባለች፣ ትፈካለች።

ህይወት የምትሸነፈው በትምህርት ብዛት ወይም ረቂቅ እውቀቶችን በመረዳትብቻ አይደለም። ኑሮን የተሻለ ለማድረግ የመጀመሪያው እርምጃ እራስን የተሻለ አድርጎ መገኘት ነው። በአካል፣ በአስተሳሰብ፣ በስነልቦና፣ የአላማ ሰው በመሆን…

Responses