ከአእምሮ ምግብነት ባሻገር

የተሻለች አገር ለመፍጠር የተመረጡ መጻሕፍትን በየትኛውም ሰዓትና ቦታ ማንበብ ከአእምሮ ምግብነት ባሻገር የተሻሉ መሪዎችን ለማውጣትና የበለጸገች አገር ለመስራት አቋራጭ መንገድ ነው ። ዓለም ላይ የተዋጣላቸው መሪዎች ብዙ ዲግሪ ያላቸው ሳይሆኑ እጅግ አንባቢዎቹ ናቸው ። ከአሜሪካው ቴዎዶር ሮዝቬልት እስከ ቻይናው ማኦ ሴቱንግ ፣ ከሌኒን እስከ ፑቲን ያሉ ተጽእኖ ፈጣሪ መሪዎች እጅግ አንባቢዎች ናቸው ። በሌሎቹም የዕውቀት መስክ ተጽእኖ ፈጣሪዎቹ አንባቢዎቹ ናቸው ።
የሚያነብ መሪ ፣ የሚያነብ ፓለቲከኛ ፣ የሚያነብ አለቃ፣ የሚያነብ አስተማሪ ፣የሚያነብ አክተር ፣የሚያነብ ደራሲ ፣ የሚያነብ አባት ፣የሚያነብ ተመራማሪ ፣ የሚያነብ ሰባኪ ፣ የምታነብ እናት ሥልጡን ሕዝብና የሠለጠነች አገር ለመፍጠር የማእዘን ድንጋይ ናቸው ። ያው የሚያነብ ሰው የተሻለ አስተሳሰብ ሳያዳብር አይቀርምና ….. የነቃና ተራማጅ ሕዝብ ቆፍጣና መሪዎችንና ሳይንቲስቶችን ይወልዳል።
የኢትዮጵያ ችግር በዘላቂነት የሚፈታው ብዛት ያለው የነቃ ተራማጅ ትውልድ መፍጠር ሲቻል ነው ። አንድ ጠቃሚ ሃሳብ እንኳን ይዞ የመጣን ብርቱ ሰው ሃሳቡን መረዳትና መግዛት የሚቻለው በተለያዩ መጽሐፍት የተሞረደ አሰላሳይ ንቁ ሕዝብ ሲኖር ነው። እኛም የካርል ማርክስን “ዳስ ካፒታልን” ፣ የአየን ራንድን ” (አትላስ ሽረግድን) ፣የዶስቶቪስኪን (ዘ ካራማዞቭ ብራዘርስን)፣ የዮቫል ኖኅ ሀራሬ መጽሐፍቶችን ፣ከነ አዳም ስሚዝ (የአገራት ብልጽግና ) እስካሁን ያሉት የምጣኔ ኃብት መጽሐፍቶችን ፣ የቴክኖሎጅ መጽሐፍቶችን፣ ጠንካራ- የስነ ልቦና ፣ የስነ-መለኮት ፣ የስነ-ጥበብ፣ የፍልስፍና ፣ የስነ ምግባርና ሌሎች የማናውቃቸውን አያሌ መጽሓፍቶችን ከውጭ ቋንቋ ወደ አገር ውስጥ ቋንቋ በመተርጎም ማንበብና የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት አለብን !

Related Articles

ህይወት በማንበብ ትዋባለች፣ ታብባለች፣ ትፈካለች።

ህይወት የምትሸነፈው በትምህርት ብዛት ወይም ረቂቅ እውቀቶችን በመረዳትብቻ አይደለም። ኑሮን የተሻለ ለማድረግ የመጀመሪያው እርምጃ እራስን የተሻለ አድርጎ መገኘት ነው። በአካል፣ በአስተሳሰብ፣ በስነልቦና፣ የአላማ ሰው በመሆን…

መጽሀፍት ክቡር ናቸው!

“የህይወታችን ትልቁ ደስታ መፀሀፍ ከማንበብ የሚገኝ ነው ብዬ በድፍረት ላውጅ እችላለሁ።ምክንያቱም መጽሐፍት ዓለምን ሁሉ የቀየሩ የስልጣኔ ዋና ቁልፎች ናቸው። ዓለም እዚህ የደረሰችው መፃሕፍት ታትመው ነው።…

Responses