ማንበብ በድንቁ*ርና ላይ ለማመጽ የሚደረግ እርምጃ ነው

ሕይወት የትናንት ፣ የዛሬ እና የነገ ድግግሞሽ ነው። እስካሁን የኖርነው ሕይወት በዚህ ድግግሞሽ ውስጥ ነው። ይኼን ድግግሞሽ ውጤታማ ለማድረግ እና ከአስልችነት ለመውጣት መጽሐፍ ወሳኝ ነገሮች ናቸው። በማንበብ ውስጥ ያልተቋረጠ ሕይወት መኖር ይቻላል። በልደት የተጀመረ ግን በሞት የማይቋረጥ፤ አድስ እና ልዩ አኗኗር። በመጽሐፍት ውስጥ ይኽ ዘለዓለማዊነት አለ። ስታነብ የዛሬን ብቻ ሳይሆን የትናንት እና የነገም ሕይወት ይኖርኻል። ይኽን ዑደት ለማስቀጠል ሦስት ነገር ማድረግ ዛሬ ማንበብ ፣ ማንበብ እና ማንበብ ብቻ። ያለፍነው ትናንት ዛሬ ነበር ፣ የምንኖረው ዛሬ ለነገ ቀድሞት የተገኘ ትናንቱ ነው።

ሁሌም ዛሬ እናንብብ ትናንት እና ነገን ለመኖር ይረዳል።
ይኽ በድንቁ*ርና ላይ ለማመጽ የሚደረግ እርምጃ ነው::!!!!!

Related Articles

ንባብ አሰላሳይ ያደርጋል

ንባብ ህሊናን አሰላሳይ ያደርጋል። የአንባቢ ኅሊና ጽልመተ ኅሊናን ታበራለች ቁረተ ልቡናን ታግላለች፡፡አለማወቅን ያህል ደዌን ትፈውሳለች፡፡አለማወቅን ያህል በሽታ ይዞ ሰው ጤነኛ ሊባል አይችልምና፡፡ አንባቢ ሰው የሐሳብ…

ህይወት በማንበብ ትዋባለች፣ ታብባለች፣ ትፈካለች።

ህይወት የምትሸነፈው በትምህርት ብዛት ወይም ረቂቅ እውቀቶችን በመረዳትብቻ አይደለም። ኑሮን የተሻለ ለማድረግ የመጀመሪያው እርምጃ እራስን የተሻለ አድርጎ መገኘት ነው። በአካል፣ በአስተሳሰብ፣ በስነልቦና፣ የአላማ ሰው በመሆን…

ንባብ አጭር የሆነችውን ሕይወት በረጅሙ ለመኖር የሚረዳ ተመራጭ መንገድ በመሆኑመጽሀፍትን እንመርምር

መጻሕፍት የረቀቀውን አጉልትው የሚያሳዩ፣የተሰወረውን ምስጢር ገልጠው የሚያስረዱ የእውቀትና የጥበብ ምንጮች ናቸው፡፡ይህንን ዘመን-ዘለቅ እውነታ በውል የተገነዘቡት አበው ‹‹ሁሉንም መርምሩ መልካሙን ያዙ›› በማለት አበክረው ይመክራሉ፡፡በምክራቸውም የማያውቁትን በጥልቀት…

Responses