ልብ ላለው ንባብ ለማወቅና ለመለወጥ ትልቅ ዕድል ነው።

ልብ ላለው ንባብ ለማወቅና ለመለወጥ ትልቅ ዕድል ነው።

ማንበብ፣ በብዙኀን መገናኛዎች ተረክ ፣ በትምህርት እና በአፈታሪክ በኩል የምናውቃትን ደብዛዛ ዓለም አጥርቶ በማሳየት አመለካከታችንን ያስተካክላል ፤ የአስተሳሰብ አድማሳችንን እያሰፋ የጠባብነት ቋጠሯችንን ያላላል፤ ከማይጨበጡ የቃላት ድርድሮች እና ከሙልጭልጭ የሐሳብ ውዥንብሮች አላቅቆ ከገሃዱ ዓለም እውነታ ጋር ያገናኛል።

… ማንበብ የሌሎችን እንድናደንቅ ዕድል ከመስጠቱም ባሻገር ራሳችንን በሌላ አንጻር እንድናይ ምቹ ሁኔታን ከመፍጠሩ ባሻገር ንቀን ለተውነው ማንነታችን ወይም የማንነታችን መገለጫዎች ዋጋ እንድንሰጥ ይቆሰቁሰናል።

ይህ ራስን፣ማንነትን፣ አብሮን ያለውን ዙሪያችንን ለማወቅና ለመለወጥ የሚረዳንን ሀይል እንጎናፀፍ የዕለቱ መልዕክታችን ነው።

Related Articles

መጽሀፍትን እንወዳጅ

“ማሰብ ካልጀመርክ የትኛዉም ሽቶ የህይወትህን መጥፎ ሽታ ሊደብቅ አይቻለዉም።”ብሏል ዲዮጋን። ማሰብ ሀይል ይሆንሃል፤ይህንን ሀይል ለመፍጠር ማንበብ ጠቃሚ ነው ። በነገራችን ላይ የኃይል መርህ የሚሰጠን የጠየቅነውን…

ህይወት በማንበብ ትዋባለች፣ ታብባለች፣ ትፈካለች።

ህይወት የምትሸነፈው በትምህርት ብዛት ወይም ረቂቅ እውቀቶችን በመረዳትብቻ አይደለም። ኑሮን የተሻለ ለማድረግ የመጀመሪያው እርምጃ እራስን የተሻለ አድርጎ መገኘት ነው። በአካል፣ በአስተሳሰብ፣ በስነልቦና፣ የአላማ ሰው በመሆን…

የህይወታችን መዓዛ

ማንበብ ለህይወታችን የሚሰጠው መዓዛ፣ የሚፈጥርልን ልዩ ስሜት፣ የሚያጎናፅፈን ነፃነት በቃላት ተሰፍሮ የሚያልቅ አይደለም። መፀሀፍት በየትኛውም ደብዛዛ ዘመን ጊዜን የማፍካት ጉልበት ያላቸው፤የህይወት ቅመም ናቸዉ። ማንበብ አንድ ከሚበራ ሻማ ላይ ወደ ሌላ ቁራጭ ሻማ ብርሀን ቢለኮስ፤ ሲበራ የነበረዉ ሻማ እንደማይጠፋ ሁሉ፤ አንባቢ ደግሞ ከንባቡ ያገኘውን እዉቀት በማካፈል በሌላ ሰዉ ህይወት ዉሰጥ የሚበራ ሻማ እንዲሆን ሀይልን ያቀዳጃል። እኛም ከበዛብን የስራ ጫና፣ ከሚፈታተነን የህይወት አዙሪት…

ንባብ አጭር የሆነችውን ሕይወት በረጅሙ ለመኖር የሚረዳ ተመራጭ መንገድ በመሆኑመጽሀፍትን እንመርምር

መጻሕፍት የረቀቀውን አጉልትው የሚያሳዩ፣የተሰወረውን ምስጢር ገልጠው የሚያስረዱ የእውቀትና የጥበብ ምንጮች ናቸው፡፡ይህንን ዘመን-ዘለቅ እውነታ በውል የተገነዘቡት አበው ‹‹ሁሉንም መርምሩ መልካሙን ያዙ›› በማለት አበክረው ይመክራሉ፡፡በምክራቸውም የማያውቁትን በጥልቀት…

Responses